ሌተናል ጀኔራል ጥጋቡ ይልማ በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አሚሶም ዋና አዛዥ ሆነው ተሹመዋል፡፡

ሌተናል ጀኔራል ጥጋቡ ካሁን ቀደም በአዛዥነት ሲያገለግሉ የነበሩትን ኡጋንዳዊ ሌተናል ጀኔራል ቢሲጋይ ኦዎዬሲግይሬን በመተካት ነው ቢሮውን የተረከቡት፡፡

ሌተናል ጀኔራሉ በመከላከያ ሰራዊት ለ34 ዓመታት ሰርተዋል፤በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትም በተለያዩ ዘርፎች አገልግለዋል፡፡

የአፍሪካ ህብረት ልዩ መልዕክተኛ እና የአሚሶም ሊቀመንበር ፍንሲስኮ ኪታኖ ማዴራ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡

‹‹ልዩ መልዕክተኛው ሌተናል ጄኔራል ጥጋቡ የተሰጣቸው ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው በሚገባ እንደሚወጡትም እተማመናለሁ›› ብለዋል፡፡ የቀድሞው አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ቢሲጋይ ኦዎዬሲግይሬን ሰላም በማስከበር ተልዕኳቸው ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦም አመስግነዋል፡፡

ሌተናል ጀኔራል ጥጋቡ ይልማ ‹‹ምንም እንኳን የተሰጠኝ ተልዕኮ ፈታኝ ቢሆንም የተሰለፍኩበትን ዓላማ ለማሳካት እሰራለሁ›› ብለዋል፡፡

Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe