ሞቃዲሾ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ የሰው ህይወት ጠፋ

የሶማሊያ የፖሊስ ክፍል በገለጸው መሰረት አንድ አጥፍቶ ጠፊ ሞቃዲሾ በሚገኘው ዋርዳ ናባዳ ወረዳ በሚገኘ መሥርያ ቤት ላይ ዛሬ ባደረሰው ጥቃት አራት ሰዎች ተገድለዋል።

በዋናው የወረዳው ጽህፈት ቤት የረመዳን ምግብ ይከፋፈል በነበረበት ወቅት አጥፍቶ ጠፊው በፈንጂ የተሞላ ቶዮታ መኪናን ነድቶ ገባበት ሲሉ እማኞች በአሜሪካ ድምጽ ላለው የሶማሊኛ ቋንቋ አግለግሎት ተናግረዋል።

ፖሊስ በፍንዳታው 9 ሰዎችቆስለዋል ሲል የዓይን ዕምናኞች ግን የቆሰሉት 30 ናቸው ብለዋል።

ዒላማ የተደረገው ህንፃ ቪላ ሶማልያ በተባለው በዋርታ ናባዳ ወረዳ የሚገኘው የፕሬዚዳንቱ ቤተ መንግሥት አጠገብ ይገኛል።

ፅንፈኛው ቡድን ዐል ሸባብ ለጥቃቱ ኃላፊነት ውስዷል።

ምንጭ፡ VOA Amharic

Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe