በህገ ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ ከ4 ሺህ 600 በላይ ተተኳሽ የክላሽ ጥይት ተያዘ

በህገ ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ ከ4 ሺህ 600 በላይ ተተኳሽ የክላሽ ጥይት ተያዘ፡፡

በትላንትናው ዕለት ከመቐለ ወደ ባህር ዳር ከተማ ሲጓጓዝ ከነበረ አይሱዙ ኤፍኤስአር መካከለኛ የጭነት ተሽከርካሪ በወልደያ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በጉምሩክ ሰራተኞች አማካኝነት በተካሄደ ፍተሻ ብዛቱ 4 ሺህ 615 የሆኑ ተተኳሽ የክላሽ ጥይቶች ተይዘዋል።

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎቹን በመደበቅ ለማሳለፍ የሞከሩ አሽከርካሪውን ጨምሮ  አራት ተጠርጣሪዎች  በቁጥጥር ስር ውለው ተጨማሪ ማጣራት እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

በወልደያ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አንድ ሳምንት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ10 ሺህ 600 በላይ ተተኳሽ የክላሽ ጥይቶች በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ከፅህፈት ቤቱ ያገኘኘው መረጃ ያመለክታል።

SourceFBC
Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe