በአፋር ክልል የአፍዴራ የጨው ዘረፋን በመቃወም የተቃውሞ ሠልፍ ተካሄደ ።
አፍዴራ ለድፍን 26 አመታት ከሐብቱ ከንብረቱ የተበዘበዘ ህዝብ ነው ። ጨው ሐብት ለዘመናት ጠራርገው የዘረፉ የቀንጅቦች አፍዴራ ጨው አሁንም በአደባባይ ለመዝረፍ በመሯሯጥ ላይ ይገኛሉ።
የቀድሞ የአፋር ክልል ፕረዚዳንት አቶ እስማኤል አሊሴሮ ከወያኔ አመራሮች ጋር በመሆን ግንባር ቀደም ፊታውራሪ ናቸው። ዛሬ ይህን ድርግት በመቃወም የቀንጅቦች ከአፍዴራ ይውጡልን ንብራታችን ወደህዝቡ ይመለስ ሠኢድ ያሲና የከዳባ ዘራፍዎች ከጨው ላይ እጃቸውን ያውጡልን በማለት የተቃውሞ ሰልፍ እየተደረገ ይገኛል። የአፍዴራ ህዝብ ድምጽ ይሰማ። የቀንጅቦች ከአፍዴራ ይውጡ። በማለት የአፍዴራ ነዋሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ታውቋል።
Source:- Mereja.com