ኢሰመኮ ስለ ኤርትራ ወታደሮች ተሳትፎ ምን ይላል?

“ኬላ” ከተሰኘው የአሐዱ ቴሌቪዥን ፕሮግራም ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተቋማቸው በትግራይ ጦርነት የኤርትራ ወታደሮች ተሳትፎ እንዳደረገ ያምናል ወይ ? ተብለው ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ተቋማቸው አሁን ላይ የምርመራው ስራ ሳይጠናቀቅ ሙሉ መደምደሚያ ላይ ላለመድረስ ጥንቃቄ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

እስካሁን በተደረገው ምርመራ በምዕራብ ትግራይ የተወሰኑ የኤርትራ ወታደሮች/የኤርትራ ወታደር ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች/በአካባቢው የተመለከቷቸው ሰዎች የኤርትራ ወታደሮች ናቸው ብለው የገለጿቸው ሰዎች መኖራቸውን እንዳረጋገጡላቸው አሳውቀዋል።

አምንነስቲ ባቀረበው የአክሱም ሪፖርት ጉዳይም ፤ ኢሰመኮ እስካሁን ባደረገው ክትትል በአክሱም በተፈፀመው ክስተት የኤርትራ ወታደሮች ተሳታፊ መሆናቸውን የሚያመላክቱ ማስረጃዎች መሰብሰባቸውን ዶ/ር ዳንኤል ገልፀዋል።

ነገር ግን የስፋቱን መጠን፣ የተሳተፉት ሰዎች ብዛትና መጠን፣ የደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት መጠን፣ የሰብዓዊ ጥሰቱ ምንነት እና አይነት ፣ የኤርትራ ወታደሮች የተሳትፎ መጠን፣ ቁጥራቸው ስንት ነው የሚለውን ኢሰመኮ ምርመራውን ስላላጠናቀቀ ዝርዝር ውስጥ መግባት እንደማይፈልግ ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል።

ኢሰመኮ እያደረገ ባለው የምርመራና የክትትል ስራ ቦታው ላይ ተገኝቶ ሳያጣራና ሳያረጋግጥ መደምደሚያ ላይ መድረስ ስለሌለበት አሁንም በምርመራ ስራው መቀጠሉን ገልጾ ፤ ኮሚሽኑ የሚደርስበትን ግኝት ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተናግረዋል።

Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe