ከ64 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን በጨለማ ውስጥ እንደሚኖሩ ተገለፀ

በሀገራችን ባሉት ዝቅተኛ የሀይል ማመንጫ ግድቦች ምክንያት ከ64 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የመብራት ተጠቃሚ አለመሆናቸውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ገልፀዋል።

ዶክተር አረጋዊ ይህንን ያሉት በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ምሁራን ለህዳሴው ግድብ ያላቸው ተሳትፎ በሚለው ጉባኤ ላይ ነው።

የመብራት አገልግሎትን ከማጣት በተጨማሪ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችን በጭስ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎች ተጋላጭ ሆነዋል ብለዋል።

ይህም ሆኖ በቂ የሆነ ለማገዶ ፍጆታ የሚሆኑ ነገሮችም ተሟልተው አያገኙም ነው ያሉት።

አሁን ከምንገኝበት ችግር ሊቀንስልን የሚችለውን የህዳሴው ግድብን በሀገራዊ ስሜት እየገነባን የምንገኘውም ለዚሁ ነው ብለዋል።

ስለሆነም ምሁራን በአባይ ወንዝ መነሻ ተፋሰስና ጣና አካባቢ የተፋሰሱን ጉልበት ሊጨምሩ የሚችሉ ጥናቶችንና ምርምሮችን ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

ጥናቶቹም የብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ብሎም የህዳሴው ግድባችን በደለል እንዳይሞላም የሚያስችሉ ሊሆኑ ይገባል ሲሉ አሳስብዋል።

SourceEthio FM
Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe