የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር 25 አባላት ያሉት አዲስ ካቢኔ አዋቀሩ

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ  25 አባላት ያሉት አዲስ ካቢኔ አዋቅረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዶክ የቀድሞ ካቢኔያቸውን ባለፈው እሁድ መበተናቸው ይታወሳል፡፡

ይህን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባዋቀሩት ካቢኔ ውስጥ  ሁለት ሚኒስትሮችን ከወታደራዊ ሀይል እና ሌሎችን ደግሞ ከቀድሞ አማጺ ቡድን አካተዋል።

ይህም ባለፈው አመት ጥቅምት ወር የተደረሰውን የሰላም ስምምነት መሰረት በማድረግ የተፈጸመ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ከዚህ ባለፈም በካቢኔያቸው ውስጥ የፍትህና እኩልነት እንቅስቃሴ የተሰኘው ቡድን መሪና የምጣኔ ሀብት ባለሙያው  ጂብሪል ኢብራሂምን የገንዘብ ሚኒስትር በማድረግ አካተዋል፡፡

በተጨማሪም የቀድሞውን የሃገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ልጅ የሆነችውን መሪያማ አል ሳዲቅ  የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር  አድርገው ሾመዋል ፡፡

አዲስ የተዋቀረው ካቢኔ ሃገሪቱ ብሄራዊ ምርጫ እስከምታካሂድበት የፈረንጆቹ 2024 ድረስ በስልጣን ላይ  የሚቆይ መሆኑም ነው የተገለጸው።

Sourceቢቢሲ
Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe