የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሳሳተና ተቀባይነት የሌለው ካርታ በመጠቀሙ ይቅርታ ጠየቀ

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሳሳተና ተቀባይነት የሌለው የአፍሪካን ካርታ በድረ ገፁ ላይ በመጠቀሙ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ሶማሊያ የሌለችበት የአፍሪካ ካርታ መጠቀሙንና በምትኩ ሶማሌ ላንድ ራሷን የቻለች አገር አድርጎ አቅርቧል ሲል ሚሞ የተባለው የሶማሊያ ሚዲያ ድርጊቱን ኮንኖታል።

መሥሪያ ቤቱ ካርታውን የተጠቀመው ባለፈው ቅዳሜ የተከበረውን የአፍሪካ ቀንን አስመልክቶ በፃፈው ጽሁፍ ላይ ነበር።

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኦፊሴላዊ ድረ ገፁ የተጠቀመው የአፍሪካ ካርታ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ግዛት እንደሆነች ተደርጎ ቀርቦበታል።

በካርታው ላይ በሶማሌ ላንድ የምትገኘው ሃርጌሳ አስተዳዳር ራሷን የቻለች አገር እንደሆነች አሳይቷል።

ካርታው በማህበራዊ ሚዲያዎች ከተዘዋወረ ከሰዓታት በኋላ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ካርታውን ከገፁ ላይ ያጠፋው ሲሆን በኢፌዴሪ አርማ ተክቶታል።

ስህተቱ በፈጠረው ውዥንብር መፀፀቱን የገለፀው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ቡድኑ የድረ ገፁን ደህንነት ለማረጋጋጥ እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፡ BBC Amharic

Kumneger Media
Kumneger Media
Kumneger Media is a News and Entertainment Website & Channel. Kumneger Media in addition to News and Entertainment it is the hub of Politics, Movies, Drama, Music, Comedy, Documentary and More!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትስስር ይፍጠሩ

325,851FansLike
49,039FollowersFollow
13,194SubscribersSubscribe