የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ባለሙሉ ፕሮፌሰሮች ካውንስል ተመስርቷል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በበይነ መረብ በመታገዝ የካውንስሉን የምስረታ ጉባዔ አካሂዷል።
የካውንስሉ ምስረታ ምሁራን ከሚኒስቴሩ ጋር በመቀናጀት የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ግቦችን ለማሳካትና በአገር ልማት አስተዋጽኦ የሚያደርጉበትን መንገድ ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።
ካውንስሉ የመምህራንና የአሰልጣኞች ልማት፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራትና አግባብነት፣ የምርምር ጥራት አግባብነትና ተደራሽነትን ጨምሮ ሰባት የትኩረት መስኮች እንዳሉትም ተገልጻል።